አሜሪካ በአውሮፓ ህብረት ላይ የ30 በመቶ ቀረጥ የምትጥል ከሆነ ህብረቱ ከነሐሴ 1 ጀምሮ ምላሽ ይሰጣል ሲሉ የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ኡርሱላ ቮን ደር ላየን ተናግረዋል።
ፕሬዚዳንቷ የአውሮፓ ህብረት ከነሐሴ 1 በፊት ከአሜሪካ ጋር ስምምነት ላይ ለመድረስ ዝግጁ መሆኑን አያይዘው ገልፀዋል።
ነገር ግን አስፈላጊ ከሆነ ህብረቱ ጥቅሞቹን ለማስጠበቅ የመከላከያ እርምጃዎችን ጨምሮ አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስድ ተናግረዋል።
ፕሬዚዳንት ትራምፕ በአውሮፓ ሕብረት እና በሜክሲኮ ላይ ጭማሪ ቀረጥ ለመጣል እቅድ መያዛቸው ይታወቃል።
