የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ሙሃማዱ ቡሃሪ በ82 አመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
ሙሃማዱ ቡሃሪ በህክምና ሲረዱ በነበሩበት በለንደን ሆስፒታል በ82 አመታቸው ህይወታቸው አልፏል።
የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ሙሃማዱ ቡሃሪ በፈረንጆቹ አቆጣጠር ከ1983 እስከ 1985 የውትድርና መሪ የነበሩ ሲሆን በኋላም ከ2015 እስከ 2023 በፕሬዚዳንትነት ተመርጠው አገልግለዋል።
በሁለቱም ወታደራዊ እና ሲቪል መንግስታት ውስጥ ያገለገሉት ሙሃማዱ ቡሃሪ በእስላማዊ ስርአት መሰረት የቀብር ስነ ስርዓታቸው እንደሚከናወን ቢቢሲ ዘግቧል።
ሙሃማዱ ቡሃሪ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ
Date:
