የአፍሪካ ልማት ባንክ ለዳሸን ባንክ የ40 ሚሊዮን ዶላር የንግድ ፋይናንስ ዋስትና ብድር አፀደቀ

Date:

የአፍሪካ ልማት ባንክ ለዳሸን ባንክ የ40 ሚሊዮን ዶላር የንግድ ፋይናንስ ዋስትና ብድር እንዳፀደቀ ዛሬ ሚያዝያ 22 ቀን 2017 ዓ.ም በዳሸን ባንክ ዋና መሳሪያ ቤት በተከናወነ ሥነሥርዓት ይፋ ተደርጓል።

አህጉራዊው የልማት ባንክ ያደረገው የዋስትና ብድር የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍን ለማጠናከር፣ አነስተኛ፣ መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን እና የሀገር ውስጥ ኮርፖሬሽኖችን ለመደገፍ ያለመ ነው ተብሏል።

የተፈቀደው የፋይናንስ ዋስትና ብድር የኢትዮጵያን የግብርና እና የማኑፋክቸሪንግ ዘርፎችን ለማነቃቃት ወሳኝ የሆኑትን እንደ ማዳበሪያ፣ ፋርማሲዩቲካል፣ የፀሐይኃይል ፓነሎች እና የእርሻ ማሽነሪዎችን ጨምሮ ሌሎች አስፈላጊ ዕቃዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ድጋፍ ያደርጋልም ተብሏል።

ዳሸን ባንክ ያገኘው ድጋፍ የገቢ እና የወጪ ንግድ ፋይናንስ መስፈርቶችን እንዲያሳልጥ በማድረግ ባንኩ የኢትዮጵያ ወሳኝ የኢኮኖሚ ዘርፎች ለመደገፍ ያለውን አቅም የሚያሳድግ እንደሆነም ተነግሯል።

በዚህ የንግድ ፋይናንስ ዋስትና ብድር መሰረት የአፍሪካ ልማት ባንክ በዳሸን ባንክ ለሚቀርቡ ክፍያ ላልተከፈለባቸው ከንግድና ፋይናንስ ጋር ለተገናኙ ሰነዶች የባንክ ፍቃድ ዋስትና እንደሚሰጥም ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...