የኢራን ተደራዳሪዎች ኢስላማባድ ፓኪስታን ገቡ

Date:


የአገሪቱ ፓርላማ አፈ ጉባዔ ሙሐመድ ጋሊባፍ ልዑካኑን እየመሩ ፓኪስታን መግባታቸውን የኢራን ሚዲያዎች ዘግበዋል።

የበረራ እንቀስቃሴዎችን የሚቆጣጠረውና የሚለየው ፍላይትራዳር24 የኢራን መንግስት ጋር ግንኙነት ያላቸው ሁለት አውሮፕላኖች IRAN04 እና IRAN05 በኢዝላማባድ አቅራቢያ ማራፋቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል።

ፓኪስታን ይህን ድርድር ማሰናዳቷ በዲፕሎማሲው ረገድ ትልቅ ስም እንደሚሆንላትም እየተነገረ ነው።

የፓኪስታኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ሸሃባዝ ሽሪፍም “ኩራቱ ለፓኪስታን ብቻ ሳይሆን ለሁሉም ሙስሊም አገራት ነው” በሚል ገልፀውታል።

የኢራን ተደራዳሪዎች የአገሪቱን ፍላጎት በትክክል የሚያስፈፅሙ ናቸው ተብሏል።

ተወካዮቹ በየራሳቸው የስራ መስክ ስመጥር በመሆናቸው የቴህራንን ጥቅሞች ዳር ያደርሳሉ የሚል እምነት ተጥሎባቸዋል።

ከፓኪስታን የሚወጡ መረጃዎች እንደሚያሳዩት የድርድሩ መሰረታዊ ነጥቦች በግልፅ ቢቀመጡም የሁለቱም አገራት ተሳታፊዎች ከየት ጉዳያቸውን እንደሚጀምሩ እስካሁን ግራ አጋቢ ሆኗል።

ከመጨረሻው የጀኔቫው ድርድር ወይስ በአዲስ መልክ ፤አሊያም ከሆርሙዝ ይከፈት እና የሁለት ሳምንታት ተኩስ አቁም ይረጋገጥ የታወቀ  ነገር የለም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...