የኢራን የኒውክሌር ጣቢያ ተመትቷል መባሉን ተከትሎ የተመድ ኒውክሌር ተቆጣጣሪ ተቋም ወታደራዊ እርምጃ እንዲቆም አሳሰበ

Date:

የተባበሩት መንግሥታት የኒውክሌር ተቆጣጣሪ ተቋም፤ ኢራን በናታንዝ ኒውክሌር ተቋም ላይ ዛሬ ጠዋት ጥቃት እንደተፈጸመባት ከገለጸች በኋላ ባውጣው መግለጫ፤ “ማንኛውንም የኒውክሌር አደጋ ስጋት ለማስወገድ” ሲባል የጦርነቱ ተሳታፊ አካላት “ወታደራዊ እርምጃ ከመውስድ እንዲቆጠቡ” አሳሰበ።

ዓለም አቀፉ የአቶሚክ ኤነርጂ ኤጀንሲ በኤክስ ገጹ ባወጣው መግለጫ፤ የኢራን የኒውክሌር ስፍራ “ዛሬ ጥቃት እንደተፈጸመበት” ከቴህራም መስማቱን ገልጿል።

“ከጣቢያው ውጭ ያለው የራዲዬሽን መጠን ላይ ምንም ዓይነት መጨመር አልተመዘገበም። ኤጀንሲው መረጃዎችን እያጣራ ነው” ሲል አስፍሯል።

አክሎም የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ራፋኤል ግሮሲ “ማንኛውንም የኒውክሌር አደጋ ለማስወገድ ወታደራዊ ተዐቅቦ እንዲደረግ በድጋሚ ጥሪያቸውን ያቀርባሉ” ብሏል።

ኢራን ከቁልፍ የኒውክሌር ተቋማቷ አንዱ በሆነው ናታንዝ ላይ ጥቃቶች እንደተፈጸሙበት ያስታወቀችው ዛሬ ቅዳሜ ጠዋት ነው።

ከመሬት ስር ከሚገኙት የኢራን የኒውክሌር ጣቢያዎች አንዱ የሆነው ይህ ስፍራ ባለፈው ሐምሌ ላይ በአሜሪካ ተደብድቦ ነበር።

ቴህራን የኒውክሌር ፕሮግራሟ ሙሉ ለሙሉ ለሰላማዊ ጥቅም የሚውል መሆኑን በመግለጽ፤ ኒውክሌር መሳሪያ እየሠራች ነው በሚል የሚቀርብባትን ክስ ውድቅ ታደርጋለች።

ይሁን እንጂ ኢራን ለሰላማዊ የኒውክሌር ኃይል ከሚያስፈልገው እጅግ በበለጠ መልኩ የጥራት ደረጃው 60 በመቶ የደረሰ ዩራኒየም አበልጽጋለች። የኢራን ዩራኒየም ለጦር መሣሪያነት ለመዋል ለሚያስፈልገው 90 በመቶ የጥራት ደረጃ የቀረበ ነው።

ጦርነቱ ከመጀመሩ ሁለት ቀናት አስቀድሞ ዋሽንግተን እና ቴህራን ስለ ኢራን የኒውክሌር ፕሮግራም እየተደራደሩ ነበር።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ምርጫ ለሰላም ግንባታ

ግዮን መጽሔት :-ለኢትዮጵያ ሰላም ምርጫ አማራጭ የሌለው መንገድ ነው።...

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከባለፈው  ዓመት የ130 በመቶ ብልጫ  አተረፈ

መጋቢት 30 በተጠናቀቀው የኩባንያው በጀት ዓመት 15.9 ቢሊዮን ብር...

በዕውቀቱ በታላቁ ዓለም አቀፍ ፌስቲቫል ላይ ተመረጠ

ዝነኛው ደራሲና ገጣሚ በዕውቀቱ ሥዩም በስፔን ባርሴሎና በሚካሄደው 41ኛው...

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...