የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኢንስቲትዩት ተማሪዎችን ተቀብሎ ማሰልጠን ሊጀምር ነው

Date:

የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኢንስቲትዩት የ12ኛ ክፍል ማለፊያ ውጤት ያመጡ ተማሪዎችን በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቀብሎ ማሰልጠን ሊጀምር መሆኑን አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ህሊና በላቸው እንደገለፁት፤ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኢንስቲትዩት በቴክኒክና ሙያ ደረጃ ተማሪዎችን ለማሰልጠን እየሰራ ይገኛል።

በ2018 ዓ.ም በደረጃ አንድ፣ ሁለትና ሶስት ተማሪዎችን ለማስተማር ፍቃድ አግኝቷል፤ በዚህም 12ኛ ክፍል ማለፍ የቻሉ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር እንደሚጀምር ተናግረዋል።

በቀጣይም በቢሾፍቱ 62 ሄክታር መሬት ላይ የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማዕከል ለመገንባት ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረው፤ ማዕከሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ሲበቃ የተቋሙን አቅምና የተማረ የሰው ኃይል ቁጥር እንደሚያሳድግ ጠቁመዋል።

ኢትዮጵያ ከመቶ ዓመት በላይ የባቡር ታሪክ ያላት ሀገር ናት ያሉት ኢንጂነር ህሊና፤ ነገር ግን የዘርፉ ዕድገት እንደተጠበቀው እንዳልሆነ ተናግረዋል።

ጋዜጣ_ፕላስ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...