የኢትዮጲያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ሁለተኛ ዙር የመጀመሪያ ጨዋታዉን በታንዛኒያ አዛም ኮምፕሌክስ ስታዲየም ከታንዛኒያ ጋር አድርጎ ሁለት ለምንም ተሸንፏል።
ሉሲዎቹ በጨዋታዉ ሙሉ ብልጫ የተወሰደባቸዉ ሲሆን በእንቅስቃሴ እረገድ እንዲሁም ደግሞ በመከላከሉ በኩል በእጅጉ ተዳክመዉ ታይተዋል።
የኢትዮጲያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን የመልሱን ጨዋታ በድሬደዋ ስታዲየም በቀጣይ ሳምንት ማክሰኞ የሚከዉን ሲሆን ከ14 አመት በኋላ ዳግም ወደ አፍሪካ መድረክ ለመመለስ ከ 3 በላይ ግቦችን አስቆጥሮ ማሸነፍ ይጠበቅበታል።
ሉሲዎቹ በመጀመሪያዉ ዙር ከሜዳቸዉ ዉጭ በዩጋንዳ 2ለ0 ተሸንፈዉ በመልሱ ጨዋታ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ይህንን ዉጤት በመቀልበስ ወደ ዚህኛዉ ዙር እንዳለፉ የሚታወስ ሲሆን በሳምንቱስ ጨዋታ ይህንን ደግመዉ ዳግም ታሪክ ይፅፉ ይሆን ወይ የሚለዉ ተጠባቂ ነዉ።
