የኢትዮጵያ ሉዓላዊ ሀብት ፈንድ የሆነው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (EIH)፣ በኢትዮጵያ ወርቅ በማምረት ላይ በሚገኘው የኖርዌይ ኩባንያ አኮቦ ማዕድን ማውጫ (Akobo Minerals AB) ላይ 3 ሚሊዮን ዶላር ኢንቨስት ማድረጉን አስታውቋል።
ይህ ኢንቨስትመንት ኢትዮጵያ በአንድ የውጭ ኩባንያ ላይ የምታደርገው የመጀመሪያው ሲሆን፣ የሀገሪቱን የኢኮኖሚ አቅጣጫ ለመቀየር ያለመ እንደሆነ ተነግሯል።
በስምምነቱ መሠረት፣ ኢ.አይ.ኤች 15 ሚሊዮን አዳዲስ አክሲዮኖችን በመግዛት በኩባንያው ላይ የ7.4% ባለቤትነት ድርሻ አግኝቷል።
የኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ብሩክ ታዬ፣ ይህ እርምጃ እስካሁን በሀገር ውስጥ ኢንቨስትመንት ላይ ብቻ ያተኮረ የነበረው ኢ.አይ.ኤች. ወደ ዓለም አቀፍ ገበያ መዘርጋት መጀመሩን ያመለክታል ብለዋል።
ይህ ተከትሎ ገንዘብ የአኮቦ ማዕድናት በሰገሌ የወርቅ ፕሮጀክት ላይ አዲስ ማዕድን ማውጫ ለመገንባት የሚያስፈልገውን ወጪ የሚደግፍ ሲሆን፣ ይህም ወርሃዊ የወርቅ ምርትን ከ5-10 ኪሎ ግራም ወደ 50-80 ኪሎ ግራም ከፍ እንደሚያደርገው ይጠበቃል።
CapitalNews
