የኢትዮጵያ የሥጋ ምርት የገበያ አቅጣጫውን ወደ ሳዑዲ ዓረቢያ አደረገ

Date:

በመካከለኛው ምሥራቅ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት የበረራ መስተጓጎል በመፈጠሩ፣ ኢትዮጵያ ወደ ተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ (ዱባይ) የምትልከው የሥጋ ምርት ሙሉ በሙሉ መቋረጡ ተገለጸ።
ቀደም ሲል ከአገሪቱ አጠቃላይ የሥጋ ኤክስፖርት 30 በመቶ የሚሆነውን የምትቀበለው ዱባይ ብትሆንም፣ በአሁኑ ወቅት ምርቱ ወደ ሳዑዲ ዓረቢያ እንዲዞር ተደርጓል።

የሥጋ አምራቾችና ላኪዎች ማኅበር ፕሬዚዳንት አቶ ከሊፋ ሁሴን እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ዱባይ በረራ ቢያቋርጥም፣ ወደ ሪያድና ጂዳ በረራዎች መቀጠላቸው ለዘርፉ እፎይታ ሆኗል።

በተለይም ወቅቱ የረመዳን ጾም በመሆኑ በሳዑዲ ዓረቢያ ያለው ከፍተኛ ፍላጎት የገበያ መጥፋቱን ተፅዕኖ እንደቀነሰው ተጠቁሟል።

ይሁን እንጂ የዱባይ ገበያ መቋረጥ በረጅም ጊዜ ሂደት በዘርፉ ላይ ከፍተኛ ጫና ሊፈጥር እንደሚችል ስጋት ተደቅኗል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...

ኧረ ፋታ ስጡን?!

መንግስት ግን" ምን ሁኑ ?" ሊለን ነው :: አጀንዳ...