የኢትዮጵያ ግብርና ሜካናይዜሽን ምርታማነትን በከፈተኛ ሁኔታ እያሳደገ እንደሆነ ተገለፀ

Date:

የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ ባለፈው የመኸር ወቅት ከታረሰው 20.5 ሚሊዮን ሄክታር መሬት ውስጥ 25 በመቶው በትራክተር መታረሱን ገልጸዋል።

ሚኒስትሩ የግብርና ሜካናይዜሽንን ለማስፋፋት መንግሥት የፖሊሲ እርምጃዎችን እንደወሰደም ጠቅሰዋል። ለአብነትም የእርሻ ማሽነሪዎች ከቀረጥ ነጻ ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው ለአርሶ አደሮች ተደራሽ መደረጋቸውን ተናግረዋል፡፡

ሚኒስትሩ አክለውም የኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ ግብዓትን በራስ አቅም በመሸፈን ለግብርናው ዘርፍ አዲስ የታሪክ እጥፋት ያመጣል ብለዋል ሲል የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቅርቡ በፓርላማ ቀርበው ከምክር ቤት አባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት፤ መንግሥት ከውጭ የሚያስገባውን የአፈር ማዳበሪያ ለመተካት የማዳበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት ማቀዱን ገልፀዋል።

@sputnik_ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...