የኢትዮጵያ ፌድራል ፖሊስ እና የኢራን ፖሊስ በትብብር መሥራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ
ስምምነቱን ኮሚሽነር ደመላሽ ገብረሚካኤል እና የኢራን የሕግ አስከባሪ ኃይሎች ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል አህመድ ረዛ መፈራረማቸውን ተቋሙ አስታዉቋል።
ሁለቱ የፖሊስ ተቋማት የመረጃ ልውወጥ ለማድረግ፣ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን በጋራ እና በትብብር ለመከላከል፣ በልምድ ልውውጥ እና በአቅም ግንባታ ሥራዎች ላይ በጋራ ለመሥራት ተስማምተዋል።
