በኦሮሚያ ክልል ከ750 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር እየተሰራጨ ነው

Date:

በኦሮሚያ ክልል ለ2017/18 ምርት ዘመን ከ750 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ለአርሶ አደሮች እየተከፋፈለ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታውቋል፡፡

በቢሮው የግብርና ግብዓት አቅርቦት ዳይሬክተር አቶ ታከለ ቁሩንዴ ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷ ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር የግብርና ግብዓት አቅርቦትን በተገቢ ሁኔታ ማሳለጥ ይገባል፡፡

በመኸር እርሻ ለአርሶ አደሩ የሚያስፈልጉ የምርጥ ዘርና ሌሎች ግብዓቶች አቅርቦትን ለማሟላት በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

የአርሶ አደሩ የምርጥ ዘር ፍላጎት እያደገ መምጣቱን ጠቁመው÷በበጀት ዓመቱ 1 ነጥብ 8 ሚሊየን ኩንታል ምርጥ ዘር ለማቅረብ ታቅዶ መሰራቱን ተናግረዋል፡፡

አሁን ላይም ከ750 ሺህ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ተሰብስቦ ለአርሶ አደሩ በመሰራጨት ላይ ይገኛል ነው ያሉት፡፡

የበቆሎ፣ ስንዴ፣ ገብስ፣ ጤፍ እና የሌሎች ሰብሎችን ምርጥ ዘር በፍጥነት ለማሰራጨት ከዩኒየኖችና እና ህብረት ሥራ ማህበራት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል፡፡

በተለይም ቅድሚያ ለሚዘራው የበቆሎ ሰብል ከ139 ሺህ ኩንታል በላይ የተለያዩ ዝርያ ያላቸው ምርጥ ዘሮችን ለአርሶ አደሩ ለማዳረስ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...