በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ለመንግሥት ከፍተኛ ግብር ከከፈሉ 10 ድርጅቶች መካከል 7ቱ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች መሆናቸው ተገለጸ።
ኢትዮ ቴሌኮም 65.84 ቢሊዮን ብር ግብር በመክፈል የዝርዝሩን አናት ሲይዝ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በ36.87 ቢሊዮን ብር እንዲሁም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ30.87 ቢሊዮን ብር ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃን ይዘዋል።
የግል እና የውጭ ኢንቨስትመንት ተቋማትን በመወከል ሄኒከን ቢራ (26.1 ቢሊዮን ብር)፣ አዋሽ ባንክ (15.77 ቢሊዮን ብር) እና ቢጂአይ ኢትዮጵያ (12.59 ቢሊዮን ብር) ከፍተኛ ግብር ከፋይ ሆነው ተመዝግበዋል።
የ10ሩ ከፍተኛ ግብር ከፋይ ድርጅቶች ሙሉ ዝርዝር፡
ኢትዮ ቴሌኮም — 65.84 ቢሊዮን ብር
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ — 36.87 ቢሊዮን ብር
የኢትዮጵያ አየር መንገድ — 30.87 ቢሊዮን ብር
ሄኒከን ቢራ — 26.1 ቢሊዮን ብር
የኢትዮጵያ መርከብና ሎጅስቲክስ — 22.2 ቢሊዮን ብር
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል — 18.31 ቢሊዮን ብር
አዋሽ ባንክ — 15.77 ቢሊዮን ብር
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት — 13.58 ቢሊዮን ብር
ቢጂአይ ኢትዮጵያ — 12.59 ቢሊዮን ብር
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን — 12.33 ቢሊዮን ብር
