የከምባታ ብሔር የዘመን መለወጫ በዓል “መሳላ” በከምባታ ዞን ዋና ከተማ ዱራሜ እየተከበረ ይገኛል።
የመሳላ በዓል በዩኔስኮ የዓለም ቅርስ ሆኖ እንዲመዘገብ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ መሆናቸውን ያስታወቀው የዞኑ አስተዳደር፤ በዓሉን ለማስተዋወቅ እየሰራ መሆኑን ጠቁሟል።
“መሳላ” በዓል ከዘመን መለወጫ በዓልነቱ ባለፈ በአካባቢው የፈጠሩ ችግሮችን በእርቅ የሚፈቱበት መሆኑ ተነግሯል።
በበዓሉ ላይ የቱሪዝም ሚንስትሯ ሰላማዊት ካሳን ጨምሮ የፌደራልና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
