የዛሬ 50 ዓመት የተፃፈው መፅሀፍ ዛሬ ይመረቃል

Date:

የዛሬ 50 ዓመት የተፃፈውና ዘንድሮ ለሕትመት የበቃው የጋዜጠኛና ደራሲ መዝገቡ አባተ መፅሐፍ ዛሬ ግንቦት 25 2017 ዓ.ም በድምቀት ይመረቃል።

ጋዜጠኛና ደራሲ መዝገቡ አባተ  በኢትዮጵያ ጠቅላይ ግዛቶች እየተዘዋወረ  ከአካባቢው ነዋሪዎች  ጠይቆ የተረዳውን መዝግቦ ያዘጋጀው መፅሀፍ ከ400 በላይ ገፆች ያሉት ሲሆን የመፅሐፉም አርታዒ የታሪክ ባለሙያ ብርሀኑ ደቦጭ ነው፡፡

መፅሐፉ ዛሬበአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ራስ መኮንን አዳራሽ ሲመረቅ የደራሲው ልጆች፣ ቤተሰቦችና ወዳጆች ይታደማሉ፡፡በተጨማሪም ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ፣ የሀገር ባለውለታዎች እንደሚገኙ ይጠበቃል።

የሁነቱ አዘጋጅ ደግሞ ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን መሆኑ ሲሆን የደራሲው ቤተሰቦችና መፅሀፉ የሕትመት ብርሀን እንዲያይ አድርገዋል፡፡

በመፅሀፉ ላይ ፕሮፌሰር ባሕሩ ዘውዴ፣ ፕሮፌሰር ሰሎሞን ሙሉጌታ እና ጋዜጠኛ ማዕረጉ በዛብህ  ፣የመፅሀፍ ግምገማ የሚያቀርቡ ሲሆን የደራሲው የመዝገቡ አባተ የሕይወት ታሪክም በልጃቸው በፀሀይ መዝገቡ አባተ እንደሚቀርብ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ደራሲ እና ጋዜጠኛ መዝገቡ አባተ  የዛሬ 14 ዐመት ሕይወቱ ያለፈ ጋዜጠኛ ሲሆት በአገራችን በሕትመት ሚድያዎች በማገልገል የሚታወቅ ነው፡፡ከሠራባቸው የህትመት ውጤቶች መካከልም ሰንደቅ አላማችን አንዱ ነው፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...