በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ውስጥ ዋነኛው የጃፓን ባለሀብት የሆነው ሱሚቶሞ ኮርፖሬሽን፣ በኢትዮጵያ የቴሌኮም ዘርፍ ላለው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት የፖለቲካ አደጋ ዋስትና ማግኘቱ ተገለጸ።
ይህ የ10 ዓመት የኢንሹራንስ ሽፋን በአፍሪካ ንግድና ኢንቨስትመንት ልማት ዋስትና (ATIDI) የተሰጠ ሲሆን፣ በጃፓን የጃፓን ኤክስፖርት እና ኢንቨስትመንት ዋስትና (NEXI) ድጋፍ ተደርጎለታል።
ይህ ስምምነት በኢትዮጵያ ውስጥ ከተደረጉ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንቶች (FDI) ትልቁ ሲሆን፣ አፍሪካ ውስጥ በጃፓን ድጋፍ ከተደረጉ ትላልቅ ፕሮጀክቶችም አንዱ መሆኑ ተጠቁሟል።
ኢንሹራንሱ የመንግስት ንብረትን መውረስ፣ የገንዘብ ልውውጥ አለመቻል እና ውልን መጣስ የመሳሰሉ የፖለቲካ አደጋዎችን ይሸፍናል ተብሏል።
CapitalNews
