የጤና አገልግሎትን ለማዘመን የቀረበው ድጋፍ

Date:

የጤና ሚኒስቴር በገጠራማው የሀገራችን ክፍሎች የሚታየውን የሕክምና አቅርቦት ችግር ለመቅረፍና የአገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል የሚያግዙ 1,183 የሞተር ሳይክሎች እና 380 የሶላር የሕክምና መገልገያ መሣሪያዎች ድጋፍ አበረከተ።

በተካሄደው የርክክብ መርሃ ግብር ላይ የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ደባ እንደገለጹት፤ ድጋፉ በተለይ በመጀመሪያ ደረጃ ጤና ተቋማት የሚታየውን የአገልግሎት መቆራረጥ ለመፍታት ያለመ ነው።

በሀገር ውስጥ የተገጣጠሙትና በፀሐይ ኃይል የሚሰሩት ሞተር ሳይክሎች የጤና ባለሙያዎች በፍጥነት ተንቀሳቅሰው አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስችሉ ሲሆን፤ ከዩኒሴፍ እና ከጋቪ የተገኙት የሶላር ኃይል አቅርቦቶች ደግሞ የኤሌክትሪክ እጥረት ባለባቸው አካባቢዎች ለሕክምና መሣሪያዎች አስተማማኝ ምንጭ ይሆናሉ።

ይህ ተግባር ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመተባበር ሁሉን አቀፍ፣ ጥራት ያለውና ፍትሐዊ የጤና አገልግሎትን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ የሚያደርገው ጥረት አካል መሆኑ ተገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...

የእግር ኳስ ዳኝነት በኢትዮጵያ

ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) ግዮን መጽሔት :- እግር ኳስ...