ዶናልድ ትራምፕ ቤንያሚን ኔታንያሁን በነጩ ቤተመንግሥት ለመቀበል ቀጠሮ ይዘዋል

Date:

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቀጣዩ ሳምንት ጁላይ 7 የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁን በዋይት ሀውስ ተቀብለው እንደሚወያዩ ተገልጿል።

ሁለቱ መሪዎች በኢራን፣ በጋዛ፣ በሶሪያ እና በአጠቃላይ በመካከለኛው ምስራቅ ቀጣና ባለው ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የትራምፕ አስተዳደር ከእስራኤል መንግሥት ጋር ያለው ግኑኝነት የጠበቀ ሲሆን፤ በጋዛ ያለውን ጦርነት ማስቆም እና በሃማስ እጅ ያሉ ቀሪ ታጋቾችን ማስለቀቅ የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ተቀዳሚ ዓላማ ነው ሲሉ የፕሬዚዳንቱ ቃል አቀባይ ካሮሊን ሌቪት ተናግረዋል።

በፈረንጆቹ ኦክቶበር 7 ቀን 2023 የጀመረው የጋዛው ጦርነት መቋጫ እንዲያገኝ አሜሪካ እየሠራች ነው ያሉት ቃል አቀባዩ፤ ጦርነቱ በሚቆምበት ዙሪያ ሁለቱ መሪዎች ውይይት ያደርጋሉ ማለታቸውን የዘገበው ሮይተርስ ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...