ዶናልድ ትራምፕ ከቬንዚዌላ ነዳጅ በሚገዙ ሃገራ ላይ የ 25 በመቶ ታሪፍ እንደሚጥሉ አስታወቁ

Date:

ትራምፕ እንዳስታወቁት ከቬንዚዌላ ነዳጅ በመግዛት ወደ ሃገሩ በሚያስገባ ማንኛውም ሃገር ላይ የ25 በመቶ ታሪፍ ይጣልበታል ብለዋል፡፡

ትራምፕ በትሩዝ ማህበራዊ ድረገጻቸው ላይ በጻፉት መልዕክት ቬንዚዌላ ከአሜሪካ ጋር እጅግ ጠበኛ ሃገር ነች ስለዚህም ከቬንዚዌላ ላይ ነዳጅ የሚገዙ ሃገራት ከአሜሪካ ጋር በሚኖራቸው የንግድ ልውውጦች ላይ 25 በመቶ ታሪፍ ይጣልባቸዋል ይህም ከ ሚያዚያ 12 ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ብለዋል፡፡

ስፔን ህንድ ሩሲያ ሲንጋፑር እና ቬተናም ከ ቬንዚዌላ ላይ ነዳጅ በመግዛት ከሚታወቁት ውስጥ ናቸው፡፡

እስከ ዛሬ ባለው ራሷ አሜሪካም ከቬንዚዌላ ነዳጅ ስታስገባ የቆየች ሲሆን ባለፈው ጥር ወር ብቻ 8 ነጥብ 6 ሚሊየን በርሜል ነዳጅ ከቬንዚዌላ አስገብታለች፡፡

ባጠቃላይ ከጥር ወር ወዲህ ሁለት መቶ ሁለት ሚሊየን በርሜል ነዳጅ አሜሪካ ከሃገሪቱ ገዝታለች ሲል የዘገበው ዩሮ ኒውስ ነው፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት በዛሬ ዕትሟ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ነሔሴ 16 2018 ዓ.ም ገበያ...

ቱርክ ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ የእስር ማዘዣ አወጣች

ቱርክ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ላይ ዓለም አቀፍ...

በመቀለ የሚካሄደው የአሸንዳ በዓል የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ተሰረዘ

በትግራይ በርካታ ታዳሚ በሚገኝበት በየዓመቱ የሚከበረው የአሸንዳ ባህላዊ በዓል...

የኢትዮጵያ ፖስታ 3 ሺሕ የሚጠጉ ቅርንጫፎቹን ወደ ባንክ ኤጀንትነት ለመቀየር እንቅስቃሴ ጀመረ

የኢትዮጵያ ፖስታ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ 3 ሺሕ በሚጠጉ ቅርንጫፎቹ...