ጋዛ ላይ በተፈጸመ ጥቃት ጋዜጠኛን ጨምሮ በርካታ ሰላማዊ ሰዎች ተገደሉ

Date:

የእስራኤል ኃይሎች በጋዛ ሰርጥ ባደረሱት ተከታታይ ጥቃቶች ቢያንስ 95 ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ።

ጥቃቱ በጋዛ ሰርጥ  በሚገኝ አንድ ካፌ፣ ትምህርት ቤት እና የምግብ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የተሰነዘሩ ሲሆን ቢያንስ 95 ሰዎች መሞታቸው  ነው የተገለጸው ።

በተፈጸሙት ጥቃቶች ከተጎጂዎች መካከል ቢያንስ 62 የሚሆኑት በጋዛ ከተማ እና በግዛቱ ሰሜናዊ ክፍል የሚገኙ ናቸው።

በተለይ በሰሜናዊ ጋዛ በሚገኘው አል-ባቃ ካፌ በተባለ የባህር ዳርቻ ምግብ ቤት ላይ የተፈጸመው የአየር ጥቃት ከፍተኛ ጉዳት አስከትሏል። ጥቃቱን ተከትሎ የወጡ ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት፣ በዚህ ካፌ ብቻ 39 ሰዎች ሲሞቱ፣ በርካቶች ቆስለዋል።

በዚህ አሰቃቂ ክስተት ህይወታቸውን ካጡት መካከል እስማኤል አቡ ሃታብ የተባለ ጋዜጠኛ ይገኝበታል። በአል-ባቃ ካፌ ውስጥ ተሰብስበው የነበሩ በርካታ ሴቶችና ህጻናትም በጥቃቱ ህይወታቸውን አጥተዋል።

የዓይን እማኞች እንደገለጹት፣ የእስራኤል ተዋጊ ጄቶች በጥቃቱ መሳተፋቸውን  ተናግረዋል ሲል አልጄዝራ ዘግቧል ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...