ጠ/ሚ ዐቢይ ከትግራይ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ አባላት ጋር ተወያዩ

Date:

ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ከትግራይ የተውጣጡ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተወከሉ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ አባላት ጋር መወያየታቸውን ገልፀዋል።

በውይይቱ በተለይም የተፈናቃዮች ጉዳይ፣ የትግራይ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚዊ ሁኔታዎች ላይ በዋናነት ምክክር የተደረገባቸው ርዕሰ ጉዳዮች እንደነበሩ ተገልጿል።

በፐብሊክ ዲፕሎማሲው አባላት በኩል በርካታ ሀሳቦች የተነሱ ሲሆን፤ መንግስት ከህዝቡ ጋር ተቀራርቦ መስራት እና ህዝባዊ የውይይት መድረኮችን ማዘጋጀቱን ሊቀጥል ይገባል የሚሉትን ጨምሮ በርካታ ጥያቄዎች ተነስተዋል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰራጩት መልዕክት ገልጸዋል።

በመልዕክቱ፤ በፐብሊክ ዲፕሎማሲው አባላት ሁሉን አቀፍ ብሄራዊ ውይይት እና የትግራይ ህዝብ ድምጽ በትክክል የሚሰማባቸው ክፍት መድረኮች መቋቋም እንዳለባቸው አሳስበዋል ብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...