ፕሬዝዳንት ጀኔራል ታደሠ የትግራይን ማዕድናት እየተበዘበዘ ነዉ አሉ

Date:

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጀኔራል ታደሠ ወረደ፣ የውጭ አካላት የትግራይን ማዕድናት እየበዘበዙ ይገኛሉ በማለት ዛሬ መቀሌ ውስጥ በዘርፉ ዙሪያ በተካሄደ መድረክ ላይ መናገራቸውን የክልሉ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ኾኖም ጀኔራል ታደሠ “የውጭ አካላት” ያሏቸውን ማዕድን መዝባሪዎች ማንነት ለይተው እንዳልጠቀሱ ተነግሯል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ የማዕድናት ምዝበራን ለመከላከል ያቋቋመው ግብረ ኃይል፣ ከሰሜን ምዕራብ ዞን ብቻ 440 የወርቅ ማውጫ ማሺኖችን ከሕገወጥ የማዕድን ቦታዎች መያዙን በመድረኩ ላይ ባቀረበው ሪፖርት መናገሩን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።

ትግራይ በተያዘው ዓመት ከወርቅ ማዕድን አውጪዎች 7 ቢሊዮን ብር ገቢ ትጠብቅ እንደነበር የጠቀሰው ግብረ ሃይሉ፣ በዓመቱ የተገኘው ግን 24 ሚሊዮን ብር ብቻ እንደሆነ ገልጧል ተብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...