ፖሊስ ከአዲስ ስታንዳርድ የወሰዳቸውን የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች በአፋጣኝ እንዲመልስ ሲፒጄ ጠየቀ

Date:

11 hours ago

በፖሊስ በተወሰዱት የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች ውስጥ የሚገኙ ከስራ ጋር የተያያዙ እና የግል መረጃዎች አላግባብ ጥቅም ላይ ሊውሉ ይችላሉ ሲል ስጋቱንም ገልጿል

ፖሊስ በአዲስ ስታንዳርድ ላይ ባደረገው ብርበራ በወሰዳቸው የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች ውስጥ የሚገኙ ከስራ ጋር የተያያዙ እና የግል መረጃዎች አላግባብ ጥቅም ላይ ሊውሉ ይችላሉ ሲል የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች የሆነው ተቋም (ሲፒጄ) ትላንት ሚያዚያ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ስጋቱን አስታወቀ።

በአዲስ ስታንዳርድ ላይ ፖሊስ እያካሄደ ያለውን ምርመራ እንዲያቋርጥ የጠየቀው ሲፒጄ፤ የተወሰዱት የተቋሙ የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎችንም በአፋጣኝ እንዲመልስ አሳስቧል።

“አዲስ ስታንዳርድ ላይ የተፈጸመው ብርበራ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የኢትዮጵያ መንግስት ነፃ ሚዲያዎችን ዝም ለማሰኘት እያካሄደው ያለው ዘመቻ አካል ነው፤ የተቋሙን የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎች መውሰዱ በውስጣቸው የሚገኙ ከስራ ጋር የተያያዙና የግል መረጃዎች አላግባብ ጥቅም ላይ ሊውሉ የሚችልበት እድል ከፍተኛ ነው” ሲሉ የሲፒጄ አፍሪካ ፕሮግራም አስተባባሪ ሙቶኪ ሙሞ ስጋታቸውን መግለጻቸውን አስታውቋል።

ስድስት የደንብ ልብስ ያልለበሱ የፖሊስ አባላት መሆናቸውን የገለጹ ሰዎች ሚያዝያ 9 ቀን2017 ዓ.ም የአዲስ ስታንዳርድን ቢሮ መበርበራቸውን፣ የዜና ክፍል ኃላፊውንና የሰው ሃብት አስተዳደር ሃላፊውን ለምርመራ ወደ ፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ መውሰዳቸውን የድርጅቱ መስራች ፀዳለ ለማ ለጋዜጠኞች መብት ተሟጋቹ ተቋሙ (CPJ) ተናግረዋል።

ፖሊሶቹ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ እንዳላቸው ቢናገሩም፣ ግልባጭ ሳያሳዩ ወደ ተቋሙ ቢሮ ዘው ብለው መግባታቸውን፤ የተቋሙ ጋዜጠኞች ሁከት ሊያስከትል የሚችል ዘጋቢ ፊልም በማዘጋጀት ተጠርጥረው ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሆነ እንደነገሯቸው ፀዳለ ተናግረዋል፡፡

አክለውም፤ ክሱ ሀሰት መሆኑንና ድርጅቱ ዘጋቢ ፊልሞችን የማዘጋጀት አቅም እንደሌለው መግለጻቸውን ሲፒጄ በመግለጫው አካቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...