10ኛው የሳይንስ ፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ ሊካሄድ ነዉ

Date:

(ሚያዝያ 13/2017 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ 10ኛዉን ከተማ አቀፍ የሳይንስ የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ ከሚያዚያ 16-18/2017 ዓ.ም ድረስ “በፈጠራ ስራ የተካነ ትጉህ ትውልድ ለሀገር ብልጽግና!” በሚል መሪ ሀሳብ ከፍተኛ የመንግስት የሰራ ሀላፊዎች ፣ የትምህርት አመራሮች ፣ የትምህርት ባለድርሻ አካላት ፣ የትምህርት ባለሙያዎች ፣ መምህራንና ተማሪዎች በተገኙበት በወዳጅነት ፓርክ ያከናውናል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ እያከናወናቸው ያሉ የትምህርት ልማት ስራዎች ፍራቸውን በሳይንስና የፈጠራ ስራ ላይ የምናይበት ብሎም በዓውደ ርዕዩ ላይ የምንመለከታቸው የተማሪዎችና የመምህራን የፈጠራ ስራዎች የሀገራችንን የፈጠራ ስራ ወደ ፊት ከፍ የሚያደርጉ እንደሚሆኑ ይታመናል፡፡

10ኛዉን ከተማ አቀፍ የሳይንስ የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ ለትውልድ ግንባታ የተሰጠውን የላቀ ትኩረት በተጨባጭ በፈጠራ ስራው ከፍ ብሎ በተግባር የሚታይበት ፤ ችግር ፈቺ ትጉ ትውልድ የሚገነባበትና ለአዲስ አበባ ሁለንተናዊ ዕድገትና ብልጽግና የሚሰሩ ጥበበኛ ወጣቶችን የምናይበት መድረክ እንደሚሆንም ይጠበቃል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫ በሚያካሂድባቸው ቦታዎች ሁሉ እሳተፋለሁ

በዘንድሮው ሀገራዊ ምርጫ እንደሚሳተፍ ያስታወቀው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማሕበራዊ ፍትህ...

በሲዳማ ክልል ከ62% በመቶ በላይ የሚታረሰው መሬት በአሲዳማነት የተጎዳ ነዉ

በኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ የሚታየው የምርታማነት ማነቆ በዋናነት የመሬት አሲዳማነት...

የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች ስብሰባ ሳይገኙ ቀሩ

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና...

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት

የኢትዮጵያ እና ሕንድ የቆየ ዲፕሎማሲዊ ግንኙነት የአፍሪካ-ሕንድ...