10ኛው የሳይንስ ፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ ሊካሄድ ነዉ

Date:

(ሚያዝያ 13/2017 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ 10ኛዉን ከተማ አቀፍ የሳይንስ የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ ከሚያዚያ 16-18/2017 ዓ.ም ድረስ “በፈጠራ ስራ የተካነ ትጉህ ትውልድ ለሀገር ብልጽግና!” በሚል መሪ ሀሳብ ከፍተኛ የመንግስት የሰራ ሀላፊዎች ፣ የትምህርት አመራሮች ፣ የትምህርት ባለድርሻ አካላት ፣ የትምህርት ባለሙያዎች ፣ መምህራንና ተማሪዎች በተገኙበት በወዳጅነት ፓርክ ያከናውናል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ እያከናወናቸው ያሉ የትምህርት ልማት ስራዎች ፍራቸውን በሳይንስና የፈጠራ ስራ ላይ የምናይበት ብሎም በዓውደ ርዕዩ ላይ የምንመለከታቸው የተማሪዎችና የመምህራን የፈጠራ ስራዎች የሀገራችንን የፈጠራ ስራ ወደ ፊት ከፍ የሚያደርጉ እንደሚሆኑ ይታመናል፡፡

10ኛዉን ከተማ አቀፍ የሳይንስ የፈጠራ ስራ አውደ ርዕይ ለትውልድ ግንባታ የተሰጠውን የላቀ ትኩረት በተጨባጭ በፈጠራ ስራው ከፍ ብሎ በተግባር የሚታይበት ፤ ችግር ፈቺ ትጉ ትውልድ የሚገነባበትና ለአዲስ አበባ ሁለንተናዊ ዕድገትና ብልጽግና የሚሰሩ ጥበበኛ ወጣቶችን የምናይበት መድረክ እንደሚሆንም ይጠበቃል፡፡

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...