15 አዲስ የተከፈቱት ቅርንጫፎች ቀጣይ ዓመት ሥራ ይጀምራሉ ተብሏል

Date:




በአገልግሎቱ ላይ የሚነሳበትን ቅሬታ ለመፍታት ላለፉት 4 ዓመታት የሪፎርም ሥራዎችን ሲሰራ የቆየው የኢሚግሬሽንና የዜግነት አገልግሎት፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 34 ነጥብ 1 ቢልዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን አስታውቋል፡፡ 

የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት “አገልግሎት አሰጣጡን ከእጅ ንክኪ ነጻ በሆነ መንገድ ለመስጠት የሚያስችል የሪፎርም ሥራ ተሰርቷል” ብለዋል።

“ተቋሙ ከአዲስ አበባ በተጨማሪ የአገልግሎት አሰጣጡን በክልሎችም እያስፋፋ ነው” ያሉም ሲሆን፤ ዋነኛ አላማውም ዜጎች ያለምንም ተጨማሪ እንግልትና ወጪ በአቅራቢያቸው በሚገኝ ቅርንጫፍ ቢሮ አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ እንደሆነ ለአሐዱ ገልጸዋል።

የተቋሙ የፓስፖርት አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ታደሰ በበኩላቸው፤ ፓስፖርት ለማውጣት የልደት ካርድ እና ዲጂታል መታወቂያ ያለው ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ያለ ቅድመ ሁኔታ አገልግሎት እንደሚያገኝ ተናግረዋል።

ማህበረሰቡ ባለማወቅ ከሕገ-ወጥ ደላሎች ጋር በመነጋገር አላስፈላጊ ድርጊት እንደሚያደርጉበት ሁኔታ መኖሩን አንስተው፤ “ከዚህን መሰል ድርጊት እራሱን መጠበቅ ይኖርበታል” ሲሉ አሳስበዋል።

በተቋሙ በተቀመጠው አሰራር መሠረት ከመደበኛ እስከ አስቸኳይ አገልግሎቱ እንደሚሰጥ የገለጹም ሲሆን፤ ሕብረተሰቡ ሁለቱን አማራጭ በመጠቀም አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችል ገልጸዋል።

አገልግሎቱን ለፈለጉ ሁሉም የሀገሪቱ ዜጎች ተደራሽ ለማድረግም 15 ቅርንጫፎች የተከፈቱበት ሁኔታ መኖሩን አንስተው፤ “እነዚህ አዲስ የተከፈቱት ተቋማት ቀጣይ ዓመት ሥራ ይጀምራሉ” ብለዋል።

እነዚህ 15 ተቋማት ከክልል ከተሞች ርቀው የሚገኙ ከተሞች ላይ መከፈታቸውን የገለጹም ሲሆን፤ ይህም ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል ተደራሽ ለማድረግ ያለመ መሆኑን አስታውቀዋል።

ለተቋሙ ችግር የሆነው በሕገ-ወጥ መንገድ አገልግሎት ማግኘት የሚፈልጉ ተገልጋዮች መበራከታቸው መሆኑን አንስተው፤ ይህን ተግባር የሚፈፅሙ ሰዎችን ከሚመለከተው አካል ጋር በመሆን የቁጥጥር ሥራ እየተሰራ መሆኑን ለአሐዱ ገልጸዋል።

አክለውም በሕገ-ወጥ መንገድ የልደት ካርድ የሚያወጡ እና ፎርጂድ ማስረጃዎችን የሚያወጡ ግለሰቦች ለተቋሙ ችግር እንደሆነበት አስታውቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ

የአርቲስት ነጻነት ወርቅነህ ስርዓተ ቀብር በመንበረ ጸባኦት ቅድስት...

በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም ዓይናቸው በጽኑ መታመሙን ጠበቃቸው ገለጹ

ከሁለት ዓመት በላይ በእስር ላይ የሚገኙት መምህርት መስከረም አበራ...

ንግድ ባንክ “ስታርፔይ” የተሰኘ አዲስ መተግበሪያ ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዲጂታል ባንክ ሥርዓቱን ይበልጥ ዘመናዊና ቀልጣፋ...

በኢትዮጵያ በካንሰር ከሚያዙ ሕፃናት መካከል 75 በመቶ የሚሆኑት ህክምና አያገኙም

በኢትዮጵያ በየዓመቱ በካንሰር ከሚጠቁ ከ6 ሺህ እስከ 8 ሺህ...