2 ሺህ 8 መቶ ህገወጥ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ ተወሰደ

Date:

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ የምስራች ግርማ የተወሰደው እርምጃ ንብረት ከመውረስ እስከ ተቋም ማሸግ መሆኑን ተናግረዋል።

ህገወጥ ንግድ ህጋዊ ነጋዴዎች ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖ ከፍተኛ በመሆኑ አንስተው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በትኩረት እየሰራ በመሆኑ በ6 ወር ውስጥ 2 ሺህ 8 መቶ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን አስታውቀዋል ።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከሚሰራው ስራ አንዱ ህገወጥ የጎዳና ንግድን መቆጣጠር መሆኑን አንስተው ከቀድሞ ጋር ሲነጻጸር መቀነሱን ተናግረዋል፡፡

የጎዳና ንግድ መቀነስ የተቻለው ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ጋር በመቀናጀት በመስራት በሰንበት ገበያዎች እንዲሳተፉ በማድረግ በህጋዊ መንገድ የንግድ ስራ እንዲሰሩ ምቹ ሁኔታ በመፈጠሩ ነው ብለዋል።

አሐዱ ራድዮ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ንባብ ለህይወት!” ታላቅ የንባብ ሳምንት እና የመጻሕፍት አውደ ርዕይ

የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት እና የንባብ ለህይወት...

በኢትዮጵያ ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ ጋር ይኖራሉ

በኢትዮጵያ ከ10 ሚልዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ እና ከ2...

የቶዮታ ኮሮላ መኪና በኤሌክትሪክ ሊመጣ ነዉ

የዓለማችን ግዙፍ የመኪና አምራች የሆነው ቶዮታ፤ እንደ ቴስላ እና...

ኢራንን ለመምታት የዩናይትድ ስቴትስ ጄቶች ከምድሯ ይነሱ እንደነበር እሥራኤል ይፋ አደረገች

የእሥራኤል መከላከያ ሚንሥትር እሥራኤል ካትስ የዩናይትድ ስቴትስ የጦር ጄቶች...