ትራምፕ በአሜሪካ የሚኖሩ የ240 ሺ ዩክሬናውያንን ህጋዊ ፍቃድ ሊሰርዙ ነው
የትራምፕ አስተዳደር ከሩሲያ ጦርነት ሸሽተው የወጡ 240 ሺ ዩክሬናውያንን ጊዜያዊ ህጋዊ ፍቃድ ለመንጠቅ ማቀዱን ሮይተርስ የትራምፕ ከፍተኛ ባለስልጣንን እና ጉዳዩን የሚያውቁ ሶስት ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል። ሮይተርስ እንደዘገበው፣ ይህ ዩክሬናውያንን የማፈናቀል ሂደት በሚያዝያ ወር ላይ እንደሚጠበቅ እና ወደ በፍጥነት ተግባራዊ ሊያደረግ ይችላል ተብሏል።
እቅዱ ከፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ ጋር ከፈጠሩት ፍጥጫ ቀደም ብሎ ነበር ተብሏል። በፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ስር ወደ አሜሪካ እንዲገቡ ወደ 1.8 ሚሊዮን ለሚጠጉ ስደተኞች የተዘረጋው ጥበቃን በመሰረዝ የትራምፕ አስተዳደር ሰፊ ስደተኞችን የማስወጣት ጥረት አካል ናቸው። ሆኖም ግን ከዋይት ሀውስ ምንም አይነት ይፋዊ ምላሽ አልተሰጠም።
የዩናይትድ ስቴትስ የሀገር ውስጥ ደህንነት ክፍል ቃል አቀባይ ትሪሲያ ማክላውሊን መምሪያው በአሁኑ ጊዜ ምንም አይነት መግለጫ አይሰጥም ብለዋል። የዋይት ሀውስ እና የዩክሬን ኤምባሲ አስተያየት እንዲሰጡ ለቀረበላቸው ጥያቄም ዝምታን መርጠዋል። በጃንዋሪ 20 የወጣው የትራምፕ ሥራ አስፈፃሚ ትዕዛዝ መሰረት በአሜሪካ ለመቆየት ፍቃድ ያጡ ስደተኞች የተፋጠነ የመባረር ሂደቶች ሊገጥማቸው ይችላል::
