ባለስልጣኑ የተሽከርካሪ ዓመታዊ የቴክኒክ ምርመራ ተቋማትን በመገምገም ነው የጎላ ክፍተት የተገኘባቸው 24 ተቋማት ላይ ርምጃ የወሰደው፡፡
በዚህ መሰረትም 2 የምርመራ ተቋማት ፈቃዳቸው የተሰረዘ ሲሆን÷ 4 ተቋማት ደግሞ ለሶስት ወራት ታግደው ክፍተታቸውን እንዲያርሙ ተወስኗል፡፡
በተጨማሪም 6 ተቋማት ለአንድ ወር ሥራ እንዲያቆሙ እንዲሁም 12 ተቋማት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው መሆኑ ተመላክቷል፡፡
በቀጣይ የመዲናዋ ነዋሪዎች ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘት እንዲችሉ በቁርጠኝት እንደሚሰራም ባለስልጣኑ አስታውቋል፡፡
