5 ሚሊየን ብር የወጣበት የድምፃዊ አቤል 4ተኛ የሙዚቃ አልበም ተለቀቀ

Date:

“ቅን” የተሠኘው የድምፃዊ የግጥምና ዜማ ደራሲ አቤል ሙሉጌታ 4ተኛ የሙዚቃ አልበም ዛሬ ከሰአት በድምፃዊው የዩቱብ ቻናል ላይ ይለቀቃል

ይህ በርካታ የሀገራችን የሙዚቃ ባለሙያዎችን ያሳተፈውና የሀገራዊ፣የማህበራዊ፣የፍቅር፣የፍልስፍናና ታሪካዊ ጉዳዮችን የሚያነሳው የሙዚቃ አልበም በዛሬው እለት ለአድማጮች በራሱ የአቤል ሙሉጌታ የዩቲዩብ ቻናል ይለቀቃል።

የድምፃዊ የግጥምና ዜማ ደራሲ አቤል ሙሉጌታ 4ተኛ አልበም 14 ትራኮችን የያዘ ሲሆን ስራውን ሰርቶ ለማጠናቀቅም 5 ዓመታትን መውሰዱ ተነግሯል፡፡

የሁሉም ትራኮች ግጥምና ዜማ በራሱ በድምፃዊው በአቤል ሙሉጌታ ሲሰሩ በቅንብር ካሙዙ ካሳ፣አቤል ጳውሎስ፣ታምሩ አማረ፣አዲስ ፍቃዱ፣ሮቤል እንዳለ፣አብርሃም ኪዳኔና ሙሳ ማቲ በሚክሲንግ ሰለምን ሃ/ማርያም፣አቤል ጳውሎስና አብርሃም ኪዳኔ በማስተሪንግ ኪሩቤል ተስፋዬ ተሳትፈውበታል፡፡

በኢትዮጵያ የሙዚቃ ኢንደስትሪ ውስጥ በርካታ ስራዎችን በመስራት ከ90ዎቹ መጨረሻ አንስቶ እጅግ ተወዳጅነትና ተቀባይነትን ያገኘው ድምፃዊ የግጥምና ዜማ ደራሲ አቤል ሙሉጌታ 4ተኛ አልበሙን ለማውጣት ዝግጅቱን ሙሉ በሙሉ አጠናቋል።

በዛሬው እለት አቤል ሙሉጌታ በተሰኘው የዩቱብ ቻናሉ ለአድማጮቹ የሚያደርስ ሲሆን በ1999 “አላማሽም” በ2003 “ተገርሜ” በ2011 “እንነጋገር” በተሰኙት የሙዚቃ አልበሞቹ በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትና ተቀባይነት ያገኘው ድምፃዊ አቤል ሙሉጌታ ለበርካታ የሀገራችን አንጋፋና ወጣት ድምፃዊያን ማለትም ፀሃዬ ዮሃንስ፣ዳዊት ፅጌ፣ብዙአየሁ ደምሴ፣ሄለን በርሄ፤ቬሮኒካ አዳነ፣ራሄል ጌቱ፣ተመስገን ገ/እግዚአብሔር፣መስፍን(ነይ በክረምት)ን ጨምሮ ለሌሎች በርካታ ድምፃውያን ተወዳጅ የሆኑ የግጥምና ዜማ ስራዎችን ሰርቷል፡፡

ድሬ ትዩብ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አርሰናል ከቦርንማውዝ በጉጉት የሚጠበቅ ጨዋታ

በ32ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ቀን...

በአሜሪካ እና ኢራን ድርድር ላይ የሚነሱ አራት ቁልፍ ጥያቄ

በፓኪስታን የሚደረገው የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር እየተጠበበፓኪስታን ነገር ግን...

መንገዳችን ረጅም፣ ጉዟችን ፈታኝ መሆኑን እናውቃለን

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤ በዓል...

የተመድ ዋና ጸሐፊ ኢራን እና አሜሪካ “በቅን ልቦና” ወደ ድርድሩ እንዲገቡ ጠየቁ

የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አሜሪካ እና ኢራን...