53 ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው መመለሳቸው ተገለጸ

Date:

መንግሥት በማይናማር በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ እና ታይላንድ ወታደራዊ ካምፕ ተጠልለው የነበሩ 53 ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ማድረጉን አስታወቀ።

መጋቢት 7 ቀን 2017 ዓ.ም 23 ዜጎችን እንዲሁም መጋቢት 8 ቀን 2017 አ.ም ደግሞ 30 ዜጎችን በአጠቃላይ በካምፑ የነበሩትን 53 ዜጎች እንዲመለሱ ማድረግ መቻሉን ገልጿል።

ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ የተደረጉት ኢትዮጵያውያኑ ከማይናማር እገታ ወጥተው ታይላንድ ወታደራዊ ካምፕ የነበሩ መሆናቸውን ጠቁሟለ።

ኢትዮጵያውያኑ ወደ ሀገራቸው እነዲመለሱ የተደረገው ከኢትዮዽያ አየር መንገድ ጋር በመተባበር እና በአካባቢው ከሚገኙ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጋር በመነጋገር መሆኑን አስታውቋል።

እስካሁን ከማይናማር እገታ ወጥተው ታይላንድ ወታደራዊ ካምፕ የነበሩ በመጀመሪያውና ሁለተኛው ዙር በጠቅላላው 130 ዜጎችን ወደ ሀገራቸው መመለስ መቻሉን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ትራምፕ የኢራን የኒውክሌር ተቋም ላይ ጥቃት ለማድረስ ዛቱ

አሜሪካ በኢራን ላይ የምታደርሰው ጥቃት 11ኛ ቀኑን ይዟል። ፕሬዝዳንት...

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የአሜሪካ ” American Space ” ማዕከል ተመረቀ

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቨን ማሲንጋ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተቋቋመውን "American...

አሐዱ ባንክ ለ 8ኛ ጊዜ የደም ልገሳ መርሐ ግብር አከናወነ

አሐዱ ባንክ ሥራ የጀመረበትን 4ኛ ዓመት በማስመልከት የተለያዩ ኩነቶችን...

ዕንባ ጠባቂ ከቀረቡለት አቤቱታዎች 84% በመንግስታዊ ተቋማት ላይ የቀረቡ ናቸው

የኢትዮጵያ ህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በተጠናቀቀው የ2018 በጅት ዓመት...