65 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

Date:

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ከፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን እና ከልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 አስተዳደር ጋር በመቀናጀት በተደረገ ልዩ ኦፕሬሽን በተቋሙ ቢሮ አካባቢ በመሆን በህገ ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 65 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አዋለ።

ተጠርጣሪዎች በተለያየ የህገ-ወጥ የድለላ ስራዎች ላይ የተሰማሩ፣ የስራ ከባቢውን በማወክ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ችግር እየፈጠሩ ያሉ፣ በተለያየ የማጭበርበር እና የማታለል ተግባር ላይ ተሰማርተው የነበሩ እና በህገ-ወጥ መንገድ የኦን ላይን የአስቸኳይ ፓስፖርት የሚሞሉ መሆናቸው ተገልፆል።

በአጠቃላይ 7 በህገወጥ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ የተሰማሩ ቤቶች መታሸጋቸውን እና 65 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር የዋሉ መሆኑ ተነግሯል። ከእነዚህም መካከል 25 ቱ ሴቶች እንደሆኑ ታውቋል።

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከባለፈው  ዓመት የ130 በመቶ ብልጫ  አተረፈ

መጋቢት 30 በተጠናቀቀው የኩባንያው በጀት ዓመት 15.9 ቢሊዮን ብር...

በዕውቀቱ በታላቁ ዓለም አቀፍ ፌስቲቫል ላይ ተመረጠ

ዝነኛው ደራሲና ገጣሚ በዕውቀቱ ሥዩም በስፔን ባርሴሎና በሚካሄደው 41ኛው...

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...