የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በአዲስ አበባ ብቻ ተወስኖ የቆየውን 905 አጭር ሥልክ ቁጥር የጥሪ ማዕከል አገልግሎት ወደ ሀገር አቀፍ ደረጃ ሊያሳድግ ነው።
አዲስ አበባ ላይ ብቻ ተወሰኖ የነበረው የደንበኞች የጥሪ ማዕከል አገልግሎት ከ2018 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ጀምሮ ሀገር አቀፍ ሊደረግ ነው።
የአገልግሎቱ የደንበኞች ግንኙነት ማዕከል ኃላፊ ስምረት በለጠ እንደተናገሩት፤ የደንበኞችን ጥሪ የመቀበል አቅም በማሳደግ የጥሪ ማዕከል አገልግሎት ሀገር አቀፍ ለማድረግ የሚያስችል አሰራር ተዘርግቷል።
ቀደም ሲል የጥሪ ማዕከሉ 905 በመባል ለአዲስ አበባ ከተማ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ደንበኞች ብቻ የጥሪ አገልግሎት ይሰጥ እንደነበር ጠቅሰው፤ ተቋሙ በ2017 በጀት ዓመት ባደረገው ሪፎርም የደንበኞች አገልግሎት ማዕከል በአዲስ መልኩ እንዲደራጅ መደረጉን ጠቁመዋል፡፡
