ማንችስተር ሲቲ በአል ሂላል ተሸነፈ

Date:

ማራኪ እንቅስቃሴ በተስተዋለበት ጨዋታ የሳዑዲ አረቢያው ክለብ 4 ለ3 በማሸነፍ የሩብ ፍጻሜ ተፋላሚ መሆኑን አረጋጧል፡፡

ሁለቱ ቡድኖች መደበኛ የጨዋታ ክፍለ ጊዜውን ሁለት አቻ ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ አሸናፊውን ለመለየት ወደ ጭማሬ 30 ደቂቃ አምርተዋል፡፡

በካምፒንግ ዎርልድ ስቴዲየም በተደረገው ጨዋታ ማርከስ ሊዮናርዶ ሁለት ግቦችን አስቆጥሯል፡፡ 

ማልኮም እና ካሊሊዱ ኩሊባሊ ደግሞ ቀሪዎቹን ግቦች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው፡፡

በርናዶ ሲልቫ፣ እርሊንግ ሃላንድ እና ፊል ፎደን የማንችስተር ሲቲን ግቦች አስቆጥረዋል፡፡

በቅርቡ ከኢንተር ሚላን ጋር ከተለያየ በኋላ ወደ ሳዑዲ አረቢያው ክለብ ያመራው ሲሞን ኢንዛጊ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ በማችስተር ሲቲ ተሸንፎ ዋንጫውን ማጣቱም ይታወሳል፡፡

የሲሞን ኢንዛጊው ቡድን አል ሂላል በሩብ ፍጻሜው ከብራዚሉ ፍሉሚነንስ የሚጫወት ይሆናል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...