12 ሀገራት የሚሳተፉብት የሴቶች የአፍሪካ ዋንጫ ነገ በሞሮኮ አስተናጋጅነት ይጀመራል፡፡
ለወራት የተራዘመው እና ለ13ኛ ጊዜ በሚካሄደው መድረክ 12 ቡድኖች በሶስት ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ነገ በመክፈቻው አስተናጋጇ ሞሮኮ ከዛምቢያ በሚያደርጉት ጨዋታ ለ21 ቀን የሚቆየው ውድድር ይጀመራል፡፡
የሴቶች አፍሪካ ዋንጫን እስካሁን ማንሳት የቻሉት ሶስት ሀገራት ብቻ ሲሆኑ ናይጄሪያ 9 ጊዜ በማሳካት ቀዳሚዋ ሀገር ናት፡፡ ዋንጫውን ኢኳቶሪያል ጊኒ ሁለት ጊዜ እንዲሁም ደቡብ አፍሪካ አንድ ጊዜ አንስተዋል፡፡
የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን (ካፍ) በቅርቡ ለውድድሩ አዲስ ዋንጫ ይፋ ማድረጉም ይታወሳል፡፡
