ቻይና ለ 74 ሀገራት ከቪዛ ነፃ ጉዞን ፈቀደች

Date:

በዚህ ዝርዝር ዉስጥ አንድም የአፍሪካ አገር አልተካተተም፡፡

ከሐምሌ 16 ጀምሮ ተግባራዊ በሚደረገው በዚ የነፃ ቪዛ ጉዞ የተፈቀደላቸው 74 ሀገራት፤ ለ 30 ቀናት ወደ ቻይና ያለ ቪዛ መጓዝ እንደሚችሉ ተነግሯል።

የሀገሪቷን የቱሪዝም ገቢ ለማሳደግ ትግበራ ላይ ይውላል የተባለው ከቪዛ ነፃ ጉዞ፤ የአፍሪካ ሀገሮችን ግን ሳያካትት ቀርቷል ።

ይህ የነጻ ቪዛ ጉዞ በኮቪድ ምክንያት የተጎዳውን የሀገሪቷን የቱሪዝም ኢንዱስትሪ በከፍተኛ ደረጃ እንዲያንሰራራ ይረዳል ተብሏል።

ሆኖም ቻይና ይህን ዕድል ለሌሎች አገራት ስትፈቅድ አንድም የአፍሪካ አገር ያለማካተቷ በአፍሪካ ያላትን ተሳትፎ ለማሳደግ በቅርብ ጊዜያት ካደረገችው ጥረት ጋር የሚቃረን ነው ሲል አፍሪካ ኒውስ ዘግቧል።

ሐምሌ 2 ቀን 2017 ዓ.ም

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...