በዳሰነች ወረዳ 34 ቀበሌዎች ‘ሙሉ በሙሉ’ በኦሞ ወንዝ ሙላት ተጥለቀለቁ

Date:

በ #ደቡብ_ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ በዳሰነች ወረዳ 34 ቀበሌዎች ‘ሙሉ በሙሉ’ በኦሞ ወንዝ ሙላት መጥለቅለቃቸውና 81 ሺህ ሰዎች መፈናቀላቸውን ነዋሪዎች እና የመንግስት ኃላፊ ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ።

“የኦሞራቴ ከተማ በውሃ ተከባለች፤ የጎርፍ መጥለቅለቁ ነገ ወይም ከነገ ወዲያ ከተማችን ሊገባ ይችላል፤ እጣፈንታችንን ቁጭ ብለን እየተጠባበቅን ነው” ሲሉ ስማቸውን እንዳይጠቀስ የጠየቁ በኦምራቴ ከተማ ነዋሪ ተናግረዋል።

ሌላኛው ስሜ ባይጠቀስ ያሉ እና በጎርፍ መጥለቅለቁ ምክንያት ተፈናቅለው ነበረሙስ በተባለ መጠለያ ተጠልለው የሚገኙ ነዋሪ በበኩላቸው፤ “የእርሻ ቦታዎችን ሁሉ ጠራርጓል። ቤቶችን አፍርሷል። ኦሞራቴ ከተማን ለመዋጥ ደግሞ አንድ ኪ.ሜ እንኳን አይሞላም የተቃረበው” ብለዋል።

ስማቸውም ሆነ የስራ ሀላፊነታቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የኦሞራቴ ከተማ የመንግስት ሀላፊ፤ የኦሞ ወንዝ ሞልቶ የቱርካና ሀይቅ ከኦሞራቴ ከተማ ከዚህ ቀደም ከነበረው 60 ኪ.ሜ ርቀት አሁን ላይ ወደ 1.3 ኪ.ሜ ርቀት ላይ መጠጋቱን ጠቅሰዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...