በአዲስ አበባ 33 ሺህ ነዋሪዎች ከጎዳና ተነስተው ወደ ቤተሰቦቻቸው ተመልሰዋል ተባለ። የአዲስ አበባ ከተማ ሴቶች፣ ሕፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የ2017 እቅድ አፈፃፀምና 2018 በጀት ዓመት የልማት እቅድ ላይ ውይይት ላይ ተወያይቷል።
በርካታ ቁጥር ያላቸው ህፃናትና ህፃናትን የያዙ እናቶች ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡ ገልጿል።
ቁጥሩ ከፍተኛ ባይሆንም ከሀገሪቷ ሁሉም ክልሎች በተለያየ ገፊ ምክንያት ወደ አዲስ አበባ እንደሚመጡም ተመላክቷል።
ተቋሙ በ2017 በጀት ዓመት 15 ሺህ የጎዳና ላይ ነሪዎችን ወደ ቤተሰቦቻቸው ለመቀላቀል ማቀዱን ገልፆ አፈፃፀሙ ግን ከዚህ እጥፍ መሆኑ ነው የተመላከተው።
(አራዳ ኤፍ ኤም)
