በኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ የመድሃኒት ምርት የገበያ ድርሻ ከ8 በመቶ ወደ 41 በመቶ ማደጉን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ፍሬህይወት አበበ አስታወቁ።
ይህ ጭማሪ የመጣው የሀገር ውስጥ የመድሃኒት አምራቾች ምርቶች በግዥ ሂደት ቅድሚያ እንዲሰጣቸው በመደረጉ እንደሆነ ሚኒስትር ዴኤታዋ ገልጸዋል።
ምንም እንኳን እድገት ቢታይም፣ ለመድሃኒት ምርት የሚያገለግሉ አብዛኛዎቹ ጥሬ እቃዎች አሁንም ከውጭ የሚገቡ መሆናቸውን ሚኒስትር ዴኤታዋ ጠቁመዋል። ይህንን ለመቀየር በሀገር ውስጥ የሚገኙ ጥሬ እቃዎች ጥቅም ላይ መዋል እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።
የአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት በበኩሉ፣ የካሳቫ ስታርች ምርት ለፋርማሲዩቲካል ኢንዱስትሪዎች ያለውን አዋጭነት የሚያሳይ ጥናት ማድረጉን ገልጿል።
