የሀገር ውስጥ የመድሃኒት ምርት የገበያ ድርሻ ወደ 41 በመቶ አደገ

Date:

በኢትዮጵያ የሀገር ውስጥ የመድሃኒት ምርት የገበያ ድርሻ ከ8 በመቶ ወደ 41 በመቶ ማደጉን የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ፍሬህይወት አበበ አስታወቁ።

ይህ ጭማሪ የመጣው የሀገር ውስጥ የመድሃኒት አምራቾች ምርቶች በግዥ ሂደት ቅድሚያ እንዲሰጣቸው በመደረጉ እንደሆነ ሚኒስትር ዴኤታዋ ገልጸዋል።

ምንም እንኳን እድገት ቢታይም፣ ለመድሃኒት ምርት የሚያገለግሉ አብዛኛዎቹ ጥሬ እቃዎች አሁንም ከውጭ የሚገቡ መሆናቸውን ሚኒስትር ዴኤታዋ ጠቁመዋል። ይህንን ለመቀየር በሀገር ውስጥ የሚገኙ ጥሬ እቃዎች ጥቅም ላይ መዋል እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።

የአርማወር ሀንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት በበኩሉ፣ የካሳቫ ስታርች ምርት ለፋርማሲዩቲካል ኢንዱስትሪዎች ያለውን አዋጭነት የሚያሳይ ጥናት ማድረጉን ገልጿል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ዘመን ባንክ ከ10 ቢሊየን ብር በላይ ያልተጣራ ትርፍ አገኝ

ዘመን ባንክ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ10.2 ቢሊየን ብር በላይ...

የ8ኛው “ንባብ ለሕይወት!” ዓመታዊ የመጻሕፍት አውደ ርዕይ ጋዜጣዊ መግለጫ

ሐምሌ 20/2018 ዓ.ምበ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት እና ንባብ ለህይወት...

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የ25 ዓመታት ሀገር አቀፍ ማስተር ፕላን ጥናት ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኃይል አቅርቦት ሥርዓት ወደ ዘመናዊና ዲጂታል...

ኢራን ላይ የተደረገው ጦርነት አሜሪካን እንዳዳከማት ባለስልጣኑ ተናገሩ

የአሜሪካው ኮንግረስ አባል ቶማስ ማሲ፣ የትራምፕ አስተዳደር በኢራን ላይ...