በለንደን ዳይመንድ ሊግ በሴቶች 5000 ሜትር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች 1ኛ እና 2ተኛ ተከታትለው ገብተዋል።
ሰባት ኢትዮጵያውያት በተሳተፉበትና እርስ በእርስ ከፍተኛ ፉክክር ባሳዩበት ውድድር መዲና ኢሳ እና ፋንታዬ በላይነህ የመጨረሻዋ መስመር ድረስ ያደረጉት እልህ አስጨራሽ ፉክክር ቀልብ የሚስብ ነበር።
አውስትራሊያዊቷ ሮዝ ዴቪስ ከኋላ ተነስታ በመምጣት በሶስተኛነት አጠናቅቃለች። የገባችበት ሰዓትም (14:31.45) በርቀቱ አዲስ የኦሽኒያ ሪከርድ ሆኖ ተመዝግቦላታል።
እስከ መጨረሻዎቹ 50 ሜትሮች ድረስ ጠንካራ ፉክክር ያደረገችው ፎቶን ተስፋዬ በአራተኛነት አጠናቅቃለች።
1ኛ. 🇪🇹 መዲና ኢሳ (14:30.57
2ኛ. 🇪🇹 ፋንታዬ በላይነህ (14:30.90)
ምስጋናው ታደሰ
