የአዋሽ ወልድያ ሃራ ገበያ የባቡር ፕሮጀክት በድጋሚ ጥገናዉን ሊቀጥል ነው

Date:

ኢትዮጵያን ከጅቡቲ ወደብ ጋር ያገናኛል የተባለው በቱርኩ ያፒ መርከዚ ተቋራጭ ከ10 ዓመት በፊት 1.7 ቢሊየን ዶላር የተመደበለት የአዋሽ ወልድያ ሃራ ገበያ የባቡር ፕሮጀክት ጉዳቱ ተጠንቶ ተለይቷል ተባለ።

በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ከፍተኛ ዝርፊያ ተፈፅሞበታል የተባለው፤ ስራውም ተቋርጦ የቆየው ይህ ፕሮጀክት እንደገና ለመቀጠልም ስራ መጀመሩ ተሰምቷል።

ባቡሩ ከጦርነት እና ግጭት ባለፈ በተፈጥሮ፤ መሬት መንቀጥቀጥ ጭምር የተወሰኑ ኪሎ ሜትሮች ጉዳት እንደደረሰበት ተረድተናል።

የዚህን ፕሮጀክት ዳግም ጀምሮ ለማጠናቀቅ ጉዳቱ እንደተለየና በእቅድ እንደተያዘ የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ህሊና በላቸው ነግረውናል።

አዋሽ ወልዲያ ሀራ ገበያ የባቡር ንጣፍ መስመር ፕሮጀክት 375 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ነው።

መስመሩ ሰሜን ምስራቅ ኢትዮጵያን ከማእከላዊ ኢትዮጵያ ጋር የሚያገናኝ ነው።

የአፋር፣ የአማራና የትግራይ ክልሎች ደግሞ ይኸው የባቡር ንጣፍ መስመር የሚያልፍባቸው ናቸው።

ኢትዮጵያን ከጅቡቲ ወደብ ጋር ያገናኛል የተባለው ይህ ባቡር በሰዓት 120 ኪሎ ሜትር እንዲወረወር ተደርጎ ዲዛይን የተደረገለት ነበር።

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…… https://www.mixcloud.com/ShegerFM/43t6/

ሸገር 102.1

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...