49 ሰዎችን አሳፍሮ የነበረ የሩሲያ አዉሮፕላን ተከሰከሰ

Date:


43 መንገደኞችንና 6 ሠራተኞችን አሳፍሮ ይበር የነበረ አንድ የሩሲያ የመንገደኞች አዉሮፕላን ሩሲያን ከቻይና ጋር በሚያውስነዉ ድንበር አካባቢ ተከሰከሰ።

አንቶኖቭ 24 (A-24) የተባለዉ አዉሮፕላን  ዛሬ ጧት ሩሲያን ከቻይና ጋር ከሚያዋስነዉ ድንበር ላይ ከምትገኘዉ ብላጎቬሽሼንስክ ከተባለችዉ ከተማ ትይንዳ ወደተባለች ሌላ ከተማ መብረር ላይ ነበር።

አዉሮፕላኑ አሳፍሯቸዉ ከነበሩት ሰዎች በሕይወት የተረፈ መኖሩ ብዙ አጠራጥሯል።አዉሮፕላኑ በወደቀበት አካባቢ ቀድመዉ የደረሱ የአደጋ ሠራተኞች በእሳት የተቃጠለ የአዉሮፕላኑን ሥብርባሪ ማግኘታቸዉን አስታዉቀዋል።

አዉሮፕላኑ ይበር በነበረበት አካባቢ «አስቸጋሪ» የዓየር ሁኔታ ነበር ከመባሉ በስተቀር የአደጋዉ ትክክለኛ መንስኤ አልታወቀም።


(ፎቶ፣-የተከሰከሰዉ አዉሮፕላን ዓይነት፣ A-24)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚያደርጉት ድርድር እስኪጠናቀቅ ድረስ የተኩስ አቁሙ መራዘሙን አስታወቁ

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፓኪስታን ጥያቄ መሠረት ከኢራን ጋር የገቡትንየተኩስ...

ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ የሚውል የ40 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ተፈቀደ

የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የልማት ክንፍ የሆነው ኢአይቢ ግሎባል (EIB...

ሃይንከን በአልኮል መጠኑ ጠንከር ያለ ቢራ ለኢትዮጵያ ገበያ አስተዋወቀ

ሃይንከን ኢትዮጵያ በእለም አቀፍ ደረጃ ዝነኛ የሆነውን ዴሰፔራዶስ (Desperados)...