“ከ3 ቢሊየን ዶላር በላይ ለማግኘት ታቅዷል” – ቡናና ሻይ ባለስልጣን

Date:

በ2018 የስራ ዘመን ከቡና፣ ሻይና ቅ/ቅመም ከ3 ቢሊየን ዶላር በላይ ለማግኘት መታቀዱን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ።

ባለፈው ዓመት በኢትዮጵያ የቡና ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ 470ሺህ ቶን ቡና በመላክ ከ2.65 ቢሊየን ዶላር በላይ የተገኘበት መሆኑ መገለጹ ይታወሳል።

የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አዱኛ ደበላ የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም እና የ2018 ዕቅድ በተገመገመበት ወቅት እንደገለጹት፥ በተያዘው በጀት ዓመት ከ600ሺህ ቶን ቡና ለገበያ በማቅረብ ከ3 ቢሊየን ዶላር በላይ ለማግኘት ታቅዷል።

ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም ለክልል የስራ ኃላፊዎች ባቀረቡት ጥሪ፤ EUDR/ አውሮፓ ህብረት ያወጣውን ከደን ጭፍጨፋ ነጻ የሆነ ምርት የመግዛት መመሪያ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ፣ በሳይንሳዊ መረጃ ላይ የተመሰረተ፣ በጥራትም ሆነ በመጠን ከፍ ያለ ቡና ወደ ገበያ ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...

በሳዑዲ በምሕረት የተለቀቁ 320 ኢትዮጵያውያን

በሳዑዲ አረቢያ የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ የምህረት አዋጅ ከተሰጣቸው 1...

አሜሪካ እና እስራኤል ደቡብ ሊባኖስን ለአገሪቱ ጦር የማስረከብ ዕቅድ

አሜሪካ ድጋፏን በሰጠችው ዕቅድ መሠረት እስራኤል እና ሊባኖስ፤ የደቡብ...

የመሬት ልማትና አስተዳደር በበጀት ዓመቱ 63 በመቶ ያህሉን ማሳካት አልቻለም

የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ሊገባደድ በተቃረበው በጀት ዓመት ለመሰብሰብ...