“ቻይናና አሜሪካ ተስማሙ?

Date:

ቻይናና አሜሪካ ለተጨማሪ ዘጠና ቀናት ታሪፍ ላለመጨመር ተስማምትዋል ተባለ። በዓለም በባለግዙፍ ኢኮኖሚዎቹ መካከል የተፈጠረው የታሪፍ ውጥረት አደጋ ይዞ ይመጣል በሚል ውይይቶች ሲደረጉ ቆይተዋል።

ቤይጂንግና ዋሽንግተን ተጨማሪ ታሪፍ እርስበርስ ”ሊጣጣሉ ” የመጨረሻው ቀን ላይ ደርሰው ነበር።

ለተጨማሪ ሶስት ወራት ታሪፍን ላለመጣል አስቀምጠውት የነበረውን ቀነ ገደብ አራዘሙት የሚል መረጃ ቅድሚያ በሲ ኤን ቢ ሲ በኩል የወጣ ሲሆን ይህም የዓለምን ኢኮኖሚ በተወሰነ መጠን ያረጋጋዋል የሚል ተስፋ ተጥሎበታል።

አገራቱ ባይስማሙ ኖሮ አሜሪካ ከቻይና በምታስገባቸው ምርቶች ላይ ከ30 በመቶ ወደ 64 በመቶ ታርፉን ከፍ ለማድረግ ትገደድ ነበር።

ቻይና በአሜሪካ ላይ ምን ያህል ታሪፍ ልትጥል እንደምትችል ግን የታወቀ ነገር አልነበርም።

በእርግጥ በአሁኑ ሰዓት ቤይጂንግ ከዋሽንግተን በምታስገባቸው ምርቶች ላይ አስር በመቶ ታሪፍ እንደጣለች ይታወቃል።

ከዋይት ሀውስ ወጣ የተባው የተስፋ መረጃ ይፋ የሆነው ዶናልድ ትራምፕ ከ90 በላይ አገራት ላይ ታሪፍ በጣሉ ማግስት ነው።

ሲ ኤን ኤንና ሲ ኤን ቢ ሲ ኒውስ ዘግበውታል።

NBCEthiopia

ሆኖ_መገኘት

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...