መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በተለያዩ ተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶች ወደ አንድ ማዕከል በማምጣት ቀልጠፋ እና ምቹ አገልግሎት ለመስጠት ወደ ሥራ የገባ ማዕከል ነው፡፡
በማዕከሉ አገልግሎት እየሰጡ ከሚገኙ ተቋማት መካከል አንዱ የሆነው የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የውጭ ሀገር ዜጎች የሥራ ፍቃድ እና የዲጂታል ኢንተርፕራይዝ ምስረታ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡
ከሥራ ፍቃድ አገልግሎቱ በተጨማሪ በማዕከሉ የሥራ ፍቃድ ማደስ፣ የሥራ ፈቃድ መተካት እና የሥራ ፈቃድ ክሊራንስ እየተሰጠም ይገኛል፡፡
በሚኒስቴሩ ብቻ እየተሰጠ የነበረው አገልግሎት በመሶብ የአንድ ማዕክል አገልግሎት በተጨማሪነት መሰጠቱ የሥራ ጫና በመቀነስ ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት እንዳስቻለ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሀገር ውስጥ ሥራ ሥምሪት ማስፋፊያ ዴስክ ኃላፊ አቶ ደጀኔ በቀለ ገልጸዋል፡፡
ዜጎች አገልግሎቱን በሚኒስቴሩ ወይም በመሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ማዕከል ቀርበው ባጠረ ጊዜ ማግኘት እንደሚችሉም ጠቁመዋል፡፡
