የሶማሌላንድ ፕሬዚዳንት ለኢትዮጵያዊያን የተለየ ጥበቃ እንዲደረግ አዘዙ

Date:

የሶማሌላንድ ፕሬዚዳንት አብዲራህማን አብዲላሂ፣ የግዛቲቷ ጸጥታ ኃይሎች ለኢትዮጵያዊያን የተለየ ጥበቃ እንዲያደርጉ ትዕዛዝ ማስተላለፋቸውን የግዛቲቷ የዜና ምንጮች ዘግበዋል።

ፕሬዝደንቱ ይህን ትዕዛዝ የሠጡት፣ ሰሞኑን ሐርጌሳ ውስጥ በአንድ ኢትዮጵያዊ ወጣት ላይ የተወሰኑ ግለሰቦች ማስፈራሪያና ዛቻ ሲያደርሱ የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል መሠራጨቱን ተከትሎ ነው።

ፕሬዝዳንቱ፣ ሶማሌላንድ ከኢትዮጵያ ጋር ሥር የሰደደ ግንኙነት እንዳላት መናገራቸውን ዘገባዎቹ ጠቅሰዋል።

የፕሬዝዳንቱን ትዕዛዝ ተከትሎ፣ ጸጥታ ኃይሎች አብዲሪሳቅ ሙሴ የተባለ በቲክቶክ ላይ በተለይ የኦሮሞ ብሄር ተወላጆች የጥቃት ሰለባ እንዲኾኑ ሲቀሰቅስ ነበር የተባለ ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውለዋል መባሉን ዋዜማ ዘግባለች።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...