ሉፍታንዛ በ2030 4000 የሚሆኑ የአስተዳደር ስራዎችን በዲጂታላይዜሽን እና በኦቶሜሽን ለመቀነስ ማቀዱን አስታውቋል።
አየር መንገዱ አንዳንድ ስራዎች ከነጭራሹ ከዚህ በኋላ አያስፈልጉም ያለ ሲሆን ስራውን የተቀላጠፈ ለማድረግ እንደ የሰው ሰራሽ አስተውህሎት ያሉ እና ሌሎችም አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እንደሚጠቀም ገልጿል።
ስራን ከማቀላጠፍ በተጨማሪ አየር መንገዱን በዚህ መንገድ ማዋቀር ትርፋማ ያደርገዋል ተብሏል።
የተለያዩ አየር መንገዶች ከኪሳራ ጋር በተያያዘ ሰራተኛ ሲቀንሱ ስፕሪት የተሰኘው አየር መንገድ በዚህ አመት ለሁለተኛ ጊዜ ኪሳራ ማስተናገዱን ተከትሎ 1800 የበረራ ሰራተኞችን ሲያሰናብት ባለፈው ሐምሌ 270 አብራሪዎችን ማባረሩ ይታወሳል።
እንደ ስዊዝ እና ብራሰልስ አየር መንገድ ያሉትን በውስጡ የያዘው የሉፍታንዛ አየር መንገድ ፊቱን ወደ ሰው ሰራሽ አስተውህሎት ማዞሩ መጪው ጊዜ ምን ሊሆን እንደሚችል ያሳየ ሆኗል።
በ2030 በአለም አቀፍ ደረጃ ከ92 ሚሊየን በላይ ስራዎች በሰው ሰራሽ አስተውህሎት የተነሳ እንደሚቀነሱ ወይም እንደሚተኩ የአለም ኢኮኖሚ ፎረም መተንበዩ ይታወሳል።
የመረጃው ምንጭ Fox News ነው።
