ኢትዮጵያ የቀይ ባህርን እንድታጣ ያደረገውን ውሳኔ ማን ወሰነ? ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው

Date:

ኢትዮጵያ የኅልውናዋ ጉዳይ የሆነውን ቀይ ባህርን እንድታጣ ያደረገውን ውሳኔ ማን ወሰነ? የሚለውን ወሳኝ ጥያቄ ማቅረብ ተገቢ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀይ ባህርን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ፣ “የቀይ ባህር ጉዳይ ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልከዓ ምድራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄ ነው ብለን እናምናለን፤ ይህንን በተረጋጋ መንገድ ማየት ያስፈልጋል” ብለዋል።

‘የኢትዮጵያን የቀይ ባህር የማጣት ውሳኔ ማን ወሰነ?’ ብለን ስንፈልግ ተቋማት አልገቡበትም፤ ይህን የሚያህል የኅልውና ጉዳይ ማን እንደወሰነ መጠየቅ ተገቢ ነው ሲሉም አክለዋል።

ኢትዮጵያ ተዘግቶባት መኖር እንደማትችል ገልጸው፣ “ለጎረቤቶቻችን መናገር የምንፈልገው ኢትዮጵያ ስታድግ ለቀጣናውም ልማት ምንጭ ትሆናለች” ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፍላጎትም በትብብር ማደግ መሆኑን ነው በማብራሪያቸው ያስታወቁት።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...