ኢትስዊች አክስዮን ማህበር ከ740 ቢሊየን ብር በላይ የገንዘብ ዝውውር አደረገ

Date:

ይህ የገንዘብ ዝውውር በ2መቶ87 ሚሊየን በላይ ግብይት የተፈፀመ ነው። ከዚህ ውስጥ ከ5መቶ77 ቢሊየን ብር በላዩ፥128.3 ሚሊየን ከአንድ የፋይናንስ ተቋም ወደ ሌላ በተደረገ የገንዘብ ማስተላለፍ የተዘዋወረ መሆኑ ተገልጿል።

ኩባንያው ይህን ያለው በ12ኛው የባለአክስዮኖች ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ነው።

የኢትስዊች አክስዮን ማህበር የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ደስታ፤ የ1ሺህ ብር አክስዮን የትርፍ ድርሻ ወደ ብር 4መቶ86 አድጓል ብለዋል።

የኩባንያው አጠቃላይ የተከፈለ ካፒታል ከ 2 ቢሊየን 5መቶ ሚሊየን መሻገሩን ተናግረዋል።

የቦርድ ሰብሳቢው የኩባንያው አመታዊ ገቢ ብር 2.2 ቢሊየን መድረሱን አስታውቀዋል።

ከታክስ በፊት ኩባንያው ያገኘው ትርፍ 1.42 ቢሊየን ብር ሆኗል ብለዋል።

በግል እና በመንግስት ሁሉም ባንኮች እንዲሁም በብሔራዊ ባንክ ባለቤትነት የሚተዳደረው አክስዮን ማህበሩ፤ በፋይናንስ ተቋማት፣ በአገር ውስጥ የክፍያ ስርዓት እና በብሔራዊ የክፍያ ስርዓት መካከል የእርስ በርስ የገንዘብ ዝውውር ስርዓት እንዲኖር ለማድረግ ይገደዳል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...