በማርበርግ ቫይረስ የአንድ ሰው ህይወት ሲያልፍ ተጨማሪ ሁለት ሰዎች ቫይረሱ ተገኝባቸዉ

Date:

በዛሬው ዕለት ከተደረጉ 13 የላብራቶሪ ምርመራዎች ተጨማሪ 2 ሰዎች ላይ የማርበርግ ቫይረስ መገኘቱን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

በዛሬው ዕለት በተደረገው ምርመራ በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠው ታማሚ ከዚህ በፊት ከተገለፀው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጂንካ ከተማ በለይቶ ማቆያ የነበሩ ሲሆኑ በተመሳሳይ ቦታም የህክምና ክትትላቸውን እያደረጉ እንደሚገኙ ሚኒስቴሩ ገልጿል።

በተጨማሪም በዛሬው ዕለት አንድ ሰው በቫይረሱ ህይወቱ ሲያልፍ በአጠቃላይ በቫይረሱ ህይወታቸው እንዳለፈ የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር አራት መድረሱ ተጠቁሟል።

በሽታው መከሰቱ ከተገለጸበት ቀን አንስቶ እስካሁን 46 የላብራቶሪ ምርመራዎች የተከናወኑ ሲሆን በአጠቃላይ ቫይረሱ በ8 ሰዎች ላይ መገኘቱ ተመላክቷል። እንዲሁም አራት ሰዎች ደግሞ በህክምና ላይ እንደሚገኙ ተጠቁሟል።

የጤና ሚኒስቴር በትናንትናው ዕለት በተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ ተጨማሪ 2 ሰዎች በማርበርግ ቫይረስ መያዛቸውን ማስታወቁ አይዘነጋም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጥቃት አድራሹ ከካሊፎርኒያ መሆኑን ትራፕ ገለፁ

ትናንት ቅዳሜ ምሽት በዋይት ሃውስ የጋዜጠኞች ማኅበር የእራት ግብዣ...

በኬንያ የመንገደኞች አውሮፕላን ከመስመሩ ወጥቶ ተከሰከሰ

ዛሬ ረፋድ ላይ በኬንያ ማንዴራ የአውሮፕላን ማረፊያ አንድ...

አቶ ጀማል አህመድ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተጨማሪ 26 ሚሊየን ብር ሰጡ

አቶ ጀማል አህመድ ባሳለፍነው ወር ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ  ከሰጠው...

“የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከል”በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሊከፈት ነው

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር "የቻይና-አፍሪካ የምርምር...